ቅዳሜ ሚያዝያ 20 ቀን 2010 | |||
45′ | ሲዳማ ቡና | 0-3 | ደደቢት |
– | 44′ ሎዛ አበራ 7′ ሰናይት ቦጋለ | ||
>’ | ኢትዮ ኤሌክትሪክ | 08:00 | አዳማ ከተማ |
– | – | ||
እሁድ ሚያዝያ 21 ቀን 2010 | |||
>’ | መከላከያ | 08:00 | ድሬዳዋ ከተማ |
– | – | ||
>’ | ሀዋሳ ከተማ | 09:00 | ቅዱስ ጊዮርጊስ |
– | – | ||
>’ | ጌዲኦ ዲላ | 09:00 | ኢትዮ ንግድ ባን |
Ethiopian Premier League and Higher League News
Saturday, April 28, 2018
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ (1ኛ ዲቪዝዮን) 12ኛ ሳምንት – ቀጥታ የውጤት መግለጫ
Friday, April 27, 2018
አርባምንጭ ከተማ በውድድር አመቱ ለሁለተኛ ጊዜ አሰልጣኝ አሰናበተ
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዘንድሮ ደካማ የውድድር ጊዜ እያሳለፈ የሚገኘውና በወራጅ ቀጠናው ውስጥ የተቀመጠው አርባምንጭ ከተማ አሰልጣኝ እዮብ ማለን ማሰናበቱ ታውቋል። የአርባምንጭ ከተማ ቦርድ ክለቡ በወልዋሎ 3-0 መሸነፉን ተከትሎ ትላንት ምሽት ተሰብስቦ ውሳኔውን እንዳሳለፈ የታወቀ ሲሆን አሰልጣኙ የተሰጣቸውን እድል በአግባቡ አለመጠቀማቸው ለውሳኔው ምክንያት መሆኑ ተገልጿል።
አሰልጣኝ እዮብ ማለ ሀዲያ ሆሳዕናን ለቀው በፀጋዬ ኪዳነማርያም ምትክ የአርባምንጭ ከተማ አሰልጣኝ ሆነው ከ3 ወራት በፊት የተሾሙ ሲሆን ቡድን ከተረከቡ በኋላ ባደረጓቸው 11 የሊግ ጨዋታዎች 4 አሸንፈው 2 አቻ ወጥተው ፣ 5 ሽንፈት አስተናግደዋል። ክለቡ በተለይ ከሜዳው ውጪ የሚያስመዘግበው ደካማ ውጤት ሲያልመው ከነበረው የወራጅ ቀጠና መራቅን እንዳያሳካ አድርጎታል። ክለቡ በቀጣይ ሌላ አሰልጣኝ የመቅጠር ፍላጎት እንደሌለው የተሰማ ሲሆን ምክትል አሰልጣኙ ማትዮስ ለማ እና ግብ ጠባቂው ጃክሰን ፊጣ እስከ ውድድር አመቱ መጨረሻ ድረስ ቡድኑን ይመራሉ ተብሏል።
አሰልጣኝ እዮብ ማለ በጉዳዩ ዙርያ ለሶከር ኢትዮጵያ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተዋል። ” ውሳኔው አስገራሚ ነው የሆነብኝ። ቡድኑን ለማሻሻል እና ካለበት ደካማ የውጤት ጉዞ ለማውጣት እየጣርኩ ባለበት ጊዜ የስንብት ውሳኔ መምጣቱ አሳዝኖኛል። ክለቡ እዚህ ችግር ውስጥ የገባው በእኔ ምክንያት ከሆነ የአርባምንጭ ህዝብ ይፍረደኝ። ጥሩ ስራ እየሰራሁ ስለነበር ደጋፊው የሚያዝንበት ውሳኔ ነው። ” ብለዋል።
Subscribe to:
Posts (Atom)
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ (1ኛ ዲቪዝዮን) 12ኛ ሳምንት – ቀጥታ የውጤት መግለጫ
April 28, 2018 ሶከር ኢትዮጵያ ቅዳሜ ሚያዝያ 20 ቀን 2010 45′ ሲዳማ ቡና 0-3 ደደቢት – 44′ ሎዛ አበራ 7′ ሰናይት ቦጋለ >’ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 08:00 አዳማ ከተማ – – ...
-
April 28, 2018 ሶከር ኢትዮጵያ ቅዳሜ ሚያዝያ 20 ቀን 2010 45′ ሲዳማ ቡና 0-3 ደደቢት – 44′ ሎዛ አበራ 7′ ሰናይት ቦጋለ >’ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 08:00 አዳማ ከተማ – – ...